ተፈናቃዮች ወደቀዬአቸው እንዲመለሱ የፌደራል መንግስቱ ሕጋዊ እና ሞራላዊ ኃላፊነቱን ይወጣ ሲል የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጥሪ አቀረበ ። ከዚህ በተጨማሪ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ባሰራጨው መግለጫ የአፍሪቃ ኅብረት፣ የአሜሪካ መንግስት እና የአውሮፓ ኅብረት የፕሪቶርያው ውል እንዲፈፀም ጫና ይፍጠሩ ብሏል።
↧


